HealthFlex
×
  • Home
  • who we are
  • What We Do
    • Catering & Lodging Service
    • Consultancy Services
    • Fitness & Wellness Service
    • Providing Trainings
    • Training Facility
      • Big Conference Room
      • Medium Hall
      • Syndicate Room
      • Training Room I
      • Training Room 2
      • Training Room 3
  • Announcements & Publication
    • Training Catalogue
    • Gallery
  • Book Now
  • Contact us

ኮካ ኮላ ኩባንያ ለማኀበሩ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል የ3 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ

April 7, 2020

በሀገራችን ከፍተኛ አደጋ አየጋረጠ የመጣውን የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ አ.ማ /ኮካ ኮላ ኩባንያ/ ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር የ3 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ፡፡

መጋቢት 28 ቀን 2012 ዓ.ም ድጋፉን አስመልክቶ በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር የኮሮና ቫይረስ ዜናን በፈረንጆቹ ታህሳስ 2019 ከተሰማበት ጊዜ አንስቶ ቫይረሱ በህዝባችን ላይ ሊያደርስ የሚችለውን አደጋ ግምት ውስጥ በማስገባት ዝግጅት እያደረገ መቆየቱን የገለፁት የማኀበሩ ዋና ፀሐፊ ዶ/ር መሸሻ ሸዋረጋ፣ በተለይም ታዋቂ የሀገሪቷ አርቲስቶችን፣ የኢትዮ ጃዝ ሙዚቃ ፈጣሪ ዶ/ር ሙላቱ አስታጥቄ፣ ደራሲ አያልነህ ሙላቱ፣ አርቲሰት አለማየሁ እሸቴ፣ ፋንቱ ማንዶየ፣ ንዋይ ደበበንና አረጋኸኝ ወራሽን እንዲሁም በሲኒማ ኢንደስትሪው ታዋቂ የሆነውን አርቲስት መኮንን ለአከን በመያዝ በከተማዋ ዋና ዋና ቦታዎች ላይ ከፍተኛ የማኀበራዊ ንቅናቄ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡

ዋና ፀሐፊው ኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ ኩባንያ ማኀበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት ለማኀበሩ ይህንን የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ገልፀው ድጋፉን አስመልክተው በመላው የቀይ መስቀል አባላቶችና በጐ ፈቃደኞች ስም አመስግነዋል፡፡ ወደፊትም ኩባንያው ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተስፋቸውን  ገልፀዋል፡፡

ማህበሩ የተገኘውን የገንዘብ እርዳታ በተለይም ከፍተኛ ቁጥር ላላቸው በመዲናዋ ጐዳናዎች ላይ ወድቀው ለሚገኙ ወጣቶች፣ ሴቶችና አዛውንቶች የምግብ ድጋፍ እንደሚውልም ተመልክቷል፡፡

በኢትዮጵያ የኮካ ኮላ ኩባንያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ዳረል ዊልሰን በበኩላቸው ኮሮና ቫይረስ በዓለማችን ታሪክ ከአሁን ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ሰብዓዊ ቀውስ እያስከተለ መሆኑን አመልክተው ኩባንያቸው ችግሩን ከግምት በመውሰድ ድጋፍ ለሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን አቅም በፈቀደ ሁኔታ ከጎናቸው እንደሚሆን ገልፀዋል፡፡

ከዚህ ጋር አያይዘው ኩባንያቸው የእጅ ማጽጃ ሳኒታይዘሮችንም ማምረትና ማከፍፈል እንደሚጀምር ገልፀው ሁሉም ኢትዮጵያዊ ቫይረሱን በትብብር ለመግታት እንዲቻል ሀኪሞች የሚሰጡትን መመሪያ መተግበር እንደሚገባም ተናግረዋል፡፡

በመጨረሻም ኢስት አፍሪካ ቦትሊንግ ልክ እንደ አሁን ቀደሙ ሁሉ ወደፊትም ከኢትዮያ ቀይ መስቀል ማኅበር ጋር ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተመልክቷል፡፡

Add Comment Cancel


Ever wondered what ERCS CCDHS Provides?

Visit our Training Facility!

Calendar

April 2020
M T W T F S S
 12345
6789101112
13141516171819
20212223242526
27282930  
« Mar   May »

Categories

  • News

Tag Cloud

Front Page

Contact Us

Ethiopian Red Cross Society-Training Institute, Nifas Silk Lafto Sub City, Woreda 10, Debrezite Road, 400 meter right to Aday Ababa Textile & Garment Factory.

+251-11-442-02-35

ercsinfo@redcrosseth.org

P.o.Box: 1541

Ras Desta Dametew Avenue, Addis Ababa, Ethiopia

Quick Links

  • Call for training
  • Providing Trainings
  • Training Catalogue

FOLLOW US

  • Facebook
  • YouTube
  • X
  • Telegram
  • Flickr
Copyright ©2025 | All Rights Reserved
Designed and Developed By Rackmint System